በእውኑ ነገ ሠላማዊ ሠልፍ እወጣለሁን ?
የዛሬ ጥያቄዬ ነው
ርእስ ነው
በነገራችን ላይ ከዚህ በፊት በተደረጉት ማንኛውም ሰላማዊ
ሰልፎች ላይ ከታክሲና በዳቦ ቤት ከሚገኙት አስር ወይም
በጥፍ የሚበልጠውን ዳቦ ለመግዛት ከመሰለፍ ውጪ ሀገራዊ
በሆነ ጉዳይ ማንኛውንም የተቃውሞ ሰልፍ የመውጣት እድል
ገጥሞኝ አያው�ቅም በ1997 የተደረገውን ሰልፍ በእድሜ
አለመድረስና አለመምረጥ ምክንያት እድሉን አጥተናል ።
ለማንኛውም
" ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል " እንደሚባል
እንደ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ አባባል የኦሮሞ ሕዝብ ለአማራ
ለሌሎች ሕዝቦች ያበረከቱት ተረት ነው ቢሉንም ጊዜው አሁን
ይመስለኛል ።
እንግዲህ እኔንም ጨምሮ መንጋው ለነግ በእውኑ ሰላማዊ
ሰልፉን እወጣለውን ? ወይንም ሰላማዊ ሰልፉን እወጣለው
የሚል ሀሳብ አለው ።
በተመሳሳይ መንጋው ይህን ሊሆን ይችላል ፡ ነውም
ለነጻነቱ ሲል ለአደን ከወጣ ነብር እራሱን የሚከላከል የዝሆኖች
መንጋ ነው ። ወይንም ውይንም ይህንንም ይመስላል ሰሞኑን
በአዲስ አበባ ሰላሙን ለማደፍረስና ሁከት ለመንዛት የተቃውሞ
ሰልፍ ያደረጉትን ሰኦች እንቃወማለን እንደሚል የገበሬን ማሳ
ለማጥፋት እንደሚሄድ አንበጣም ይሆናል ።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ነገ ስለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ
አበባ ፖሊስ በebc መግለጫ ሰጥቶል ።
ማንም ቢሆን የተቃውሞ ሰልፍ ለመውጣት የተዘጋጁ
ተቃዋሚኦችን ብትመለከቱ ለሚመለከተው አካል አስታውቁ
የሚል (ቃል በቅል ባልገለብጠውም ) እኔ ምለው እንደ አዲስ
አበባ ነዋረነቴ የአዲስ አበባ ፖሊስን ለመተባበር "ሰላማዊ
ሰልፉ ላይ ቀይ ካርድ ይዤ እየወጣው ነው " እደግመዋለው
ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የቀይ ካርድ ይዤ " እየወጣው ነው ብዬ
በእራሴ ላይ ልጠቁም ነውን ?
ለመሆኑ በየትኛው አዋጅ ወይንም በየትኛው ሕግ ነው ሰላማዊ
የሆነን የተቃውሞ ሰልፍን ለመውጣት ፍቃድን ከሚመለከተው
አካል እሚጠየቀው ?
ምክንያቱም በነጻነት የመንቀሳ�ቀስ መብት የለኝም
ሀሳቤን በነጻነት እየገለጽኩኝ አይደለም
ላለ ሕዝብ ለጠየከኝ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት ፈቃድ
ሰጥቼሀለው ማለት በነጻነት የመንቀሳቀስ መብትህን አሳጥቼህ
ነበር አሁን አንስቼልሀለው ማለት ይመስለኛል።
እንደ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም " የወልቃይት ነገር "
ጽሁፍ
በዚሕ ጽሁፍ ፕሮፌሰር ለጽሁፋቸው መነሻ አንድ ሀሳብ ያነሣሉ "
ሚስትህን መምታት አቆምክ ...? " የሚል ያልተገባ ጥያቄ ።
አኦ ካልክ ወንጀል ሰርተሀል ያስጠይቅሀል አይ ካልክ ደግሞ
ወንጀል እየሰራህ ነው ። እንዲሁ ያሳስራል ።
የሚመለከተውን አካልም የሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ፍቃድ
መጠየቅ እንዲሁ ነው ። የሚመለከተው አካል ፍቃድ መስጠት
እስካሁን ስጨቁናቹ ነበር ። "ዶሮን ሲያታልሎት አርዝመው
አሰሮት " አይነት እንሁንላቹ ማለት ነው በአንጻሩ ፍቃድ
አልሰጠውም ማለት ደግሞ አሁንም ጨቆኝ ነኝ ማለት ነው ።
በእውኑ እኔ ነገ ሰላማዊ ሰልፍ እወጣለውን ?
የሚለውን ጥያቄ የቀሰቀሰው እንዲህ የሚል ጥያቄ በው
ለምን አልወጣውም ጊዜውስ መቼ ነው ?
ምክንያቱም ያለ መንጋው ሕብረት ምንም አይነት ለውጥ
እንደማይመጣ አምናለሁ ነገር ግን ተስፋ ለሌለው ሀሳብ
ከመንጋው መጉደል አልፈልግም ።
ስለዚህ ሕዝብ ነኝ የሕዝብ ጥያቄ ይመለከተኛል።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ