ኅዳር 12 ቀን ማኅሌት
እንኳን አደረሰንበዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል እግዚአብሔር በመልአኩ
በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት ሕዝቡን ከግብጽ ከባርነት ቤት
በማስወጣት ወደ ተስፋ ሀገረ ወደ ከነዓን እንዲገቡ ማድረጉን
እና የእሥራኤል ዘሥጋ ነፃ መውጣትን ፣ ቅዱስ ሚካኤል
ዱራታኦስን እና ቴውብስታን ስለ መርዳቱ ፣ መስፍነ እሥራኤል
ኢያሱን ለመርዳት መገለጡን እንዘክራለን፡፡
ይህ የነጻነት በዓል ለአዲሲቷ እሥራኤል፤ የቅድስት ቤተ
ክርስቲያን መንፈሳዊ ጉዞ እና ነጻነት ምሳሌ ሲሆን፡፡ በዚያ ዘመን
እሥራኤል ዘሥጋን በመንፈሰ ረድኤት እየረዳቸው፣ በዕደ
መልአኩ እየጠበቃቸው፣ በሙሴ እየመራቸው፣ ጠላት
እያጠፋላቸው፣ ከተስፋዋ ምድር እንዲገቡ እንዳደረጋቸው ሁሉ
በግብጽ በተመሰለች በዓለም ያለነው ክርስቶሳውያን
ምእመናንንም ዐይን ያላያትን፣ ጆሮ ያልሰማትን፣ የሰው ልብም
ያላሰባትን፣ እግዚአብሔር ለባለሟሎቹ ያዘጋጃትን አማናዊት
ከነዓን ይህችውም መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ የበቃን ሆነን
እንድንገኝ በመልአክህ ኃይል ሰውረን፣ ጠብቀን፣ አድነን በማለት
ምሳሌውን በማሰብ አማናዊውን ጉዞ ደግሞ በማስቀጠል
በረከት የምናገኝበት በዓል ነው፡፡
የእሥራኤል ረዳታቸው ቅዱስ ሚካኤልም በጥበቃው በጸሎቱ
ከእኛ እንዳይለይ ፤ ርግብ በከፍታ ሥፍራ ሆና በምድር
የወደቀችውን ቅንጣት ዘር እንደምትመለከት ሁሉ ካለህበት
ሥፍራ ከዓለመ መላእክት ሆነህ እያንዳንዳችንን ተመልከተን ፤
ጸሎታችን አሳርግልን ከሰይጣንም ማታለል ጠብቀን በማለት
የምንለምንበት የተወደደች ዕለት ናት፡፡
መልክዓ ሥላሴ
1
ሰላም ለጒርኤክሙ ስቴ አንብዓ ሰብእ ዘኀሠሠ፤
ብዑላነ ሞገስ ሥላሴ ኢታንድዩኒ ሞገሰ፤
እመ ትትሄየዩኒሰ ወተኀድጉኒ ጽኑሰ፤
ሚካኤልኑ ለአምጽኦ ሥጋየ ጌሠ
ወእመ አኮ ገብርኤል ወኀበኒ ነፍሰ፡፡
ትርጉም ፡- [አብ ወልደ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፤ ስለ ጥልቅ ንስሐ
የተነሳሕያንን የንስሐ ዕንባ ስቴን (መጠጥ) ለሚሻ ጉርዔያችሁ
ሰላምታ ይገባል፤(ሕዝ 18፡32) ሥሉስ ቅዱስ ሆይ የባለሟልነት
ባለጸጋ ናችሁና ከባለሟልነታችሁ አታውጡኝ፡፡ ከባለሟልነት
አውጥታችሁ በቸልታ ከተመለከታችሑኝማ ሚካኤል ገስግሶ
ሥጋዬን ለማስገኘት ይሆንለታልን ? ወይስ ገብርኤል በክንፉ
ከንፎ የነፍስን ሕይወት ሊሰጠኝ ይቻለዋልን ክሂሎት የእናንተ
ብቻ ነው፡፡]ጐሥዓ ልብየ ጥበበ ወልቡና ፤
ዚቅ
አመ ይፈጥራ እግዚአብሔር ለምድር፤
ኢዜነዎ ለሰማይ ወኢተማከረ ምስለ መላእክቲሁ፤
ወተከለ ሠለስተ ዕፀ ሕይወት በዲበ ምድር፤
እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕፁቂሃ፤
ዘሠናየ ጽጌ ደንጐላት ወጥዑመ ይፈሪ ሲሳዮሙ ለቅዱሳን፡፡
ነግሥ
2
ለውዳሴከ ጥዑመ ዜና፤
ቅዱስ ሚካኤል ልማድከ ግብረ ትኅትና ፤
አንተኑ ዘመራሕኮሙ ፍና፤
ወአንተኑ ለእሥራኤል ዘአውረድከ መና፤
ዚቅ
አዝነመ ሎሙ መና ይብልዑ፤
ፀዓዳ ከመ በረድ ወርእየቱ ከመ ተቅዳ፤
ኅብስተ እምሰማይ ወሀቦሙ፤
አውሐዘ ሎሙ ማየ ሕይወት፤
ዘትረ ኰኵሕ ፈልፈለ ነቅዓ ዘኢይነጽፍ ፤
ኅብስተ እምሰማይ ወሀቦሙ፡፡
3
ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ፤
ወልደ ያሬድ ኄኖክ በከመ ጸሐፈ ፤
ሶበ እጼውዕ ስመከ ከሢትየ አፈ፤
ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ፤
ለረዲኦትየ ነዓ ሰፊሐከ ክንፈ፡፡
ትርጉም ፡- [ የያሬድ ልጅ ኄኖክ እንደጻፈው ከልዑል ስም
አጠራር ጋር ለተባበረ ስምህ አጠራህ ሰላም እላለሁ፡፡
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ሆይ የተቸገረቱን የተጨነቁትን
ዘውትር እንደምትረዳቸው ሁሉ እኔንም ለመርዳት ክንፍህን
ዘርግተህ ፈጥነህ ድረስልኝ፡፡]
ዚቅ
ውእቱ ሚካኤል መልአከ ኃይል ፤ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር፤
ይሰአል ለነ ረዳኤ ይኩነነ አመ ምንዳቤነ፤
ሰፊሆ ክነፊሁ ይጸልል ዲቤነ፡፡
3
ሰላም ለልሳንከ በነቢበ ጽርፈት ዘኢተሀበለ ፣
በእንተ ሥጋሁ ለሙሴ አመ ምስለ ሰይጣን ተበሀለ
ሚካኤል ክብርከ እምክብረ መላእክት ተልዕለ
ቀዊምየ ቅድመ ሥዕልክ ሶበ አወትር ስኢለ
በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዐኒ ቃለ፡፡
ትርጉም ፡- [ስለ ሙሴ ሥጋ ከሰይጣን ጋር ክርክር በተደረገ
ጊዜ የዘለፋን ቃል ላልተናገረው አንደበትህ ሰላም እላለሁ፡፡
ክቡር መልአክ ሆይ ክብርህ ከመላእክት ሁሉ ክብር ከፍ ያለ
ነውና፤ በሥዕልህ ፊት ቁሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ሁሉ
እሽ በማለት ፈጥነህ ቃልህን አሰማኝ፡፡] (የሐዋርያው የቅዱስ
ይሁዳ መልእክት ቁ. 9)
ዚቅ
ረሰዮ እግዚኡ ፡ ለውእቱ ሚካኤል ፤
እምኵሎሙ መላእክት ይትሌዓል መንበሩ ፡፡
4
ሰላም ለሕንብርትከ፡ ሕንብርተ መንፈስ ረቂቅ፤
ዘቱሳሔሁ መብረቅ፤
ነግሀ ነግህ አንተ በአዝንሞ መና ምውቅ ፤
በገዳም ዘሴሰይኮሙ ለነገደ ኅሬ ደቂቅ፤
ሴስየኒ ሚካኤል ሕገከ ዘጽድቅ፡፡
ዚቅ
ባሕረ ግርምተ ፡ ገብረ ዓረፍተ ወበውስቴታ አርአየ ፍኖተ፤
በእደ መልአኩ ዓቀቦሙ በገዳም ለሕዝቡ አርብዓ ዓመተ፤
ወሴሰዮሙ መና ኅብስተ ፡ ኪነ ጥበቡ ዘአልቦ ዘአልቦ
መስፈርተ፡፡
5
አምኃ ሰላም አቅረብኩ ለመልክእከ ኲሉ፤
ለለ አሐዱ አሐዱ ዘበበክፍሉ፤
ሚካኤል ክቡር ለልዑል መልአከ ኃይሉ፤
ተወኪፈከ አምኃየ እምኑኀ ሰማያት ዘላዕሉ፤
ዕሴተ ጸሎትየ ፈኑ ወአስብየ ድሉ፡፡
ትርጉም ፡- [ ሚካኤል ሆይ ለእያንዳንዱ በየ ክፍሉ ለተነገሩ
መልኮችህ ሁሉ የምስጋና እጅ መንሻ አቀርባለሁ፡፡ ልዑል
መልአክ ሆይ እግዚአብሔር ኃይሉን የሚገልጽብህ ኃያል
መልአክ ነህና የምስጋናዬን እጅ መንሻ ተቀብለህ ከላይ
ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት የጸሎቴን ዋጋ እጥፍ ድርብ አድርገህ
ላክልኝ፡፡]
ዚቅ
ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ፤
ወስእለተነ ከመ መዓዛ ሠናይ፤
ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ፡፡
+++
ምልጣን
ውእቱ ሚካኤል መልአከ ኃይል ፤ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር፤
ይሰአል ለነ ረዳኤ ይኩነነ አመ ምንዳቤነ፤
ሰፊሆ ክነፊሁ ይጸልል ዲ
እስመለዓለም
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል
አስተምር ለነ ሰዓልናከ በአሰርቱ ወአርባእቱ ትንብልናከ
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል
ዐይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ ሐመልማለ ወርቅ
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል
ይሰግድ በብረኪሁ እስከ ይመጽእ ስርየት ለኀጥአን
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ክቡር መኑ ከማከ ልዑል
አስተምር ለነ ሰዓልናከ በአሰርቱ ወአርባእቱ ትንብልናከ
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል
ዐይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ ሐመልማለ ወርቅ
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል
ይሰግድ በብረኪሁ እስከ ይመጽእ ስርየት ለኀጥአን
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ክቡር መኑ ከማከ ልዑል
ሰላም
መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል፤
ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ
መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል፤
ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ