ሐሙስ 13 ኦገስት 2015

የኔ መንገድና ጥያቄዬ


ከብዙዎች ዓለም ሕልም አለ ሕልማቸውን የሚያዩበት
እንቅልፍም እንዲሁ፡ ሕልማቸው የቀን ጥያቄአቸውና
ምኞታቸው ነው ስጋዊ ተስፋቸው ብዙዎች ሕልም
መመልከቻ እንቅልፍና አልጋ ይኖራቸው ይሆናል ጥቂቶች
ግን መተኛትም ማለም ሰልችቶቸዋል ምክንያቱም ሕልም
የሚረዳ ሕዝብና ሕልም የሚተረጉም �ፈጣሪ የለምና ።
በበረከት በላይነህ ድርሰት እያዩ ፈንገ�ስ እያዩ ሕልም
ከመፍታት ሕልም ማሰርን መርጦ " የተፈታ ሕልም
እናስራለን አዳሚ የልጅነት ሕልሜ ላገሬ ማልምላት
ምናምን ትያለሽ" ይላል እያዩ እብድ ነው እያዩ መጣያ ቦታ
ይልተ�ሰጠው ቆሻሻ ነው ለዚሕም ነው " ሠው እንዴት
ቆሻሻውን መጣያ ያጣል" የሚል እያዩ ለሰኦች እብድ
እንጂ ጤነኛ ነው እብድ ያለው የቀበሌው ሊቀመንበር
እንጂ ጤነኛ ነው ።
ጥቂቶቻችን ለብዙዎች እንዲሁ ነን እብዶችና ሰነፎች እኛ
ግን ጤነኞችና ብርቱኦች ነን ። የእያዩ ጥያቄ ብዙ ነው
የእያዩ ተጠያቂም እንዲሁ �ፈጣሪ፣ መንግስት ፣ ህዝብ
እንዲሁ እራሱን ነው ።
የኛም የኔም ጥያቄም እንዱሁ ነው ፍትሕን ለሚያውቅ
ሕዝብን ሁሉ ብቻውን ለሚገ�ዛ አምላክ እንደልቤ
የሚሆነው የጠላትን እጅ በእኔ እጅ ስር ከጣልክ ከቤቴ
ስመለስ መጀመርያ ያገኘሁትን መሰዋት እደርጋለሁ ብሎ
አፋን በመልካም ከፍቶ አፋን እንደከፈተ እድያ ድንግል
የሆነች ሴት ልጁን መሰዋት ካደረገ ዮፍታሄ ይልቅ
ባልጀራውን ኦርየንን አስገድሎ ሚስቱ ቤርሳቤህን እግብቶ
የዘሞተው ዳዊት ነው ።
ለዚሕም ይመሥለኛል ጥቂቶች የዝችን ዓለም ጣእምን
የሚንቁት ( አሥተውሉ ጥቂቶች እልኩኝ እንጂ ሰማእታት
አላልኩም ) ታድያ አለምን ሁሉ ለሚገዛ ለዚሕ አምላክ
ነው ጥያቄ ከዮፍታሔ ይልቅ ለአብርሐም ተለዋጭ
መስዋትን ለሰጠ ከዮፍታሔ ይልቅ ዳዊትን እንደልቤ ላለ ።
መልካምን አድርገህ ሳለ ለምን ምልካምን ሰው
ትነጥቃለህ የምል ለብዙኦች የእንዲሕ አይነት ጥያቄ እና
እርሶን ( ሴትን (ትግስትን) ) እስከ መሞሸርያ አንድ ቀን
መጠበቅ እብደት የሆነው ።
እኔ ግን እንደጽላጦስ "ከማምንበት ነገር በላይ የሚቀርበኝ
የለም "
እላለሁ
በዚሁሉ ነገር እና መሰል እንቅፋቶች እንደጥቂቶች ሕልም
ማለም ባልፈልግም እንደ አቢሜሌክ ግን ጥፋትን
ላለማየት ብዙ ዘመናትን መተኛት እፈልጋለሁ ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ